Skip to main content

የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሥልጣንና ተግባር

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ስራ አስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 195/2015 መሠረት ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የሚከተሉት ስልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፡-

  • የወጣቶች መብትና ጥቅም በማስከበር ዙሪያ ግንዛበና ንቅናቄ እንድፈጠር ያደርጋል

  • የወጣቶችን ሁኔታ የሚያመላክቱ ዝርዝር መረጃዎችን ይሰበስባል ያደራጃል በሚመለከታቸው ሁሉ እንዲታወቅ ያደርጋል፣

  • ወጣቶች በክልሉ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ለመሳተፍና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችላቸው እድሎች የተመቻቸላቸው መሆኑን ያረጋግጣል፣

  • ወጣቶች እንደ ፍላጎታቸው ተደራጅተው ለመብቶቻቸው እንድታገሉና ችግሮቻቸውን ማስወገድ እንዲችሉ ያበረታታል ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣

  • ወጣቶች በልማት፣ መልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ላይ ንቁ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስልት ይቀይሳል ድጋፍ ይሰጣል፣

  • የወጣቶች አደረጃጀቶችን አቅም ለማጎልበት የሚያስችሉ ጥናቶችን ያካህዳል፣ ስልጠናዎችን ይሰጣል፣ የስልጠና አገልግሎት የሚሰጥበትን አሰራር ያመቻቻል፣ ያስተባብራል፣

  • በክልላችን የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ተግባራትን ያስተባብራል፣ ይመራል ፣ጥናት ያደርጋል በመላው ህዝባችን ዘንድ ባህል ሆኖ እንዲወጣ ጥረት ያደርጋል፤

  • ወጣቶች በስነምግባር የታነጹና አውንታዊ አመለካከት እንዲያጎለብቱ የስብዕና ግንባታ ስራዎች ይሰራል፣ያስተባብራል አሉታዊና መጤ ባህሎች እንዲጠበቁ ይሰራል፣

  • ወጣቶች ማዕከላትን በማስፋፋት ወጣቶች ተገቢውን መረጃ እንዲያገኙ እምቅ ችሎታቸውንና ዝንባለያቸውን እንዲያወጡበት ድጋፍ ያደርጋል፣ ይከታተላል፣ ያስተባብራል፣

  • በክልሉ ለሚንቀሳቀሱ ስፖርት ማህበራት ፈቃድ ይሰጣል፣ ይሰርዛል፣ ፕሮግራማቸውን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣

  • የስፖርት ውድድሮች እንዲዘጋጅ ያደርጋል ያስተባብራል፣

  • በክልሉ ስፖርት ማህበራት መካከል የሚነሱ ክርክሮችን በስፖርት ምክርቤት እንዲዳኝ ያደርጋል፣

  • የባህል ስፖርት እንዲታወቅና እንዲዘወተር ያደርጋል፣

  • የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንዲዘጋጁ ያደርጋል የቴክኒክ ድጋፍ ይሰጣል፣

  • የስፖርት ትምህርትና ስልጠና እንዲስፋፋ ያደርጋል

  • በግል ለሚቋቋሙ የስፖርት ስልጠና ማዕከላት ፈቃድ ይሰጣል፣ ይመዘግባል፣ ይሰርዛል

  • ለስፖርት ልማት ዕድገት የሚሆን የገቢ ምንጭ እንዲፈጠር የተለያዩ ስልቶችን ይቀይሳል፣ 

  • ክልላዊ የውድድርና የስፖርት ማህበራት ደንብና መስፈርት ያዘጋጃል፣

  • የስፖርት ጉዳይን በሚመለከት መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር የሚደረጉ  ግንኙነቶችን ስተባብራል

  • ዓላማውን ለማስፈፀም የሚረዱ ሌሎች ተግባሮችን ያከናውናል፡፡